Loading...

News and Events

የፌቤላ የመኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካ ከደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና ከደብረ ብርሃን ዩንቨርሲቲ ጋር የ3ዮሽ ሰምምነት ተፈራረመ።

📅 2025-11-13 11:38:47(24 days ago)

በላይነህ ክንዴ ግሩፕ የፌቤላ የመኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካ ከደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና ከደብረ ብርሃን ዩንቨርሲቲ ተመርቀው የወጡ ሰላሳ ሰልጣኞችን ተቀብሎ የተግባር ስልጠና ለመስጠት ስምምነት አድርጓል። ስምምነቱ ፋብሪካው ከ2ቱ ተቋማት የመለመላቸውን ሰልጣኞች ለ4 ወራት አሰልጥኖ ለመቅጠር መሆኑም ተገልጿል። በመርሐ ግብሩ ላይ የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት እንዳሉት፤ በከተማው ወደ ማምረት የገቡ ብዙ ፋብሪካዎች ቢኖሩም የበላይነህ ክንዴ ግሩፕ ግን ሞዴል የሚሆን ተግባር እየፈጸመ ነው። በዚሁ ወቅት እንዳሉት ፋብሪካው ለአካባቢውን ወጣቶች የስራ እድል ከመፍጠር አኳያ ሀላፊነቱን እየተወጣ እንደሚገኝ ገልጸዋል። እንደዚህ አይነት የኢንደስትሪ ትስስሮች ተማሪዎች በተቋማቸው ከሚያገኙት የንድፈ ሀሳብ ስልጠና በተጨማሪ የተግባር ስልጠና ለማግኘት የሚያስችል ስለመሆኑ አንስተዋል። ይህንን ተግባር ሌሎች በከተማው የሚገኙ ኢንደስትሪዎች በተሞክሮነት በመውሰድ ሰልጣኞችን በመቀበል የተግባር ስልጠና እንዲያገኙ ማድረግ እንደሚገባቸውም አስገንዝበዋል። የበላይነህ ክንዴ ግሩፕ የፌቤላ ኢንዱስትሪያል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ እንየው ዋሴ እንደተናገሩት፤ ፋብሪካው የ2ቱን ተቋማት ሰልጣኞች የንድፈ ሀሳብ ስልጠና በመስጠት በቅጥር ለመውሰድና በሌሎች ስራዎች ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የማስቻል ስራ እየሰራ ነው ኢንዱስትሪውን ለማሳደግ ባለሙያው መሰልጠን ያለበት ከዩንቨርስቲና ከቴክኒክ ኮሌጅ ብቻ ሳይሆን ከኢንዱስትሪ ተቋማትም የተግባር ስልጠና መውሰድ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ባሻዬ በየነ እንደተናገሩት፤ በኮሌጁ የሰለጠኑ ሰልጣኞች ከሰለጠኑ በኋላ ወደ ኢንዱስትሪው እንዲገቡ ለማድረግ ይህ አይነት ስምምነት ያስፈልጋል። በሰልጣኞቹ የጋራ ስራ መስራት ስላለብንና ብቁ እንዲሆኑ ኢንዱስትሪው የራሱ ድርሻ አለበት ያሉ ሲሆን 2ቱም ባለድርሻ በመሆን እንሰራለን ብለዋል።

Notice image for  የፌቤላ የመኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካ ከደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና ከደብረ ብርሃን ዩንቨርሲቲ ጋር የ3ዮሽ ሰምምነት ተፈራረመ።
Notice image for  የፌቤላ የመኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካ ከደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና ከደብረ ብርሃን ዩንቨርሲቲ ጋር የ3ዮሽ ሰምምነት ተፈራረመ።
Notice image for  የፌቤላ የመኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካ ከደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና ከደብረ ብርሃን ዩንቨርሲቲ ጋር የ3ዮሽ ሰምምነት ተፈራረመ።
Notice image for  የፌቤላ የመኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካ ከደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና ከደብረ ብርሃን ዩንቨርሲቲ ጋር የ3ዮሽ ሰምምነት ተፈራረመ።
Notice image for  የፌቤላ የመኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካ ከደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና ከደብረ ብርሃን ዩንቨርሲቲ ጋር የ3ዮሽ ሰምምነት ተፈራረመ።
Notice image for  የፌቤላ የመኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካ ከደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና ከደብረ ብርሃን ዩንቨርሲቲ ጋር የ3ዮሽ ሰምምነት ተፈራረመ።
Notice image for  የፌቤላ የመኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካ ከደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና ከደብረ ብርሃን ዩንቨርሲቲ ጋር የ3ዮሽ ሰምምነት ተፈራረመ።

በደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና ደብረ ብርሃን ከተማ ስር የሚገኙ ኢንዱስትሪዎች በትብብር ለመስራት የሚያስችል የጋራ ውይይት ተካሄደ፡፡

📅 2025-11-13 11:36:40(24 days ago)

የውይይቱ ዓላማ ኢንዱስትሪዎች ከቴክኒክና ሞያ ሰልጣኞች ሰልጥነው በሚወጡበት ሞያ ላይ በስልጠና በግብዓትና በገንዘብ በኩል ድጋፍ የሚያደርጉበትን ሁኔታ ለመግባባት እንዲሁም ከቴክኒክና ሞያ ኮሌጁ ሰልጣኞች በምን ዘርፍና ሞያ መሰልጠን እንዳለባቸው( የኢንዱስትሪዎችን ፍላጎት) ላይ መሆኑም ተመላክቷል፡፡ የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ባሻዬ በየነ እንደተናገሩት፤ ቴክኒክና ሞያ ኮሌጁ ከኢንዱስርሪዎች ጋር የሚያደርገው የጋራ ውይይት ወሳኝ ጉዳይ ነው፡፡ ኢንዱስትሪውም በክህሎት ላይ የትብብር ስልጠና እንዲሰጥ፣ ሰልጣኞች ማሽኖችን በተገቢው እንዲውቁ የራሳቸው ሚና እንዳላቸውም አስረድተዋል፡፡ ተቋማትና ኢንዱስትሪዎች በጋራ መክረው ያሉትን ክፍተቶች በመለየት የጋራ ምክር አድርገናን ብለዋል፡፡በውይይቱም ቴክኒክና ሞያ ኮሌጆች የሚያወጧቸው ሰልጣኞች ኢንዱስትሪዎች የሚፈልጉበትን አግባብ ያቀረቡ መሆኑንና ተቋሙም መረዳቱን ተናግረዋል፡፡ የአማራ ክልል ስራ ክህሎት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አማራ አለሙ እንደተናገሩት፤ የቴክኒክና ሞያ ኮሌጅ የንድፈ ሃሳብ ትምህርትን ከኢንዱስትርዎች የተግባር ትምህርት ጋር በማገናኘት ጥራት ያለው ሰልጣኝ ማውጣት ያስፈልጋል ከ40 በላይ የኢንዱስትሪ ባለቤቶች በውይይቱ መሳተፋቸውን የገለፁ ሲሆን፤ በዚህ ግንኙነት መሰረት ሰልጥነው የሚወጡ ወጣቶች የክሎት ክፍተት እንደማይኖራቸውም አስረድተዋል፡፡ ሰልጣኞች በቀጣሪ ድርጅቶች ፊት ቀርበው በሞያቸው  እንዲያሰለጥኑ እድል ማግኘታቸውና የስራ እድልም እንደሚፈጠርላቸው መደረጉ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል፡፡ የተስፋ ኢንተርፕራይዝ ድርጅት ፕሪጀክት ማናጀር ስራ አስኪያጅ አቶ ፍሬው ደሳለኝ እንደገለፁት፤ ኢንዱስትሪዎችና ቴክኒክና ሞያ ኮሌጆችን አንድ ላይ በማድረግ የስልጠና ጥራት እንዲሻሻል ስራዎችን እየሰራ ይገኛል ውይይቱ ቴክኒክና ሞያ ኮሌጆች ከኢንዱስትሪዎች ጋር ተቀራርበው እንዲሰሩ ለማድረግ ያለመ ሲሆን በዚህ መልኩ 2ቱ በስምምነት ሰልጣኖችን እንዲያበቁና የስራ እድል እንዲፈጥሩ የሚያግዝ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡ ድጅቱ በደብረ ብርሃን ከተማ በዚህ ዓመት ከ5 ሺ በላይ ወጣቶችን በተለያዩ ብድርና ስልጠና የሚደግፍ መሆኑንም አስረድተዋል ድርጅቱ በ5 ዓመት ጊዜ ውስጥ በክህሎት ስልጠና ላይ 200ሺ ወጣቶችን እንደ ሀገር ለማሰልጠን ያቀደ ሲሆን ግማሽ ጊዜውን አጠናቋል ብለዋል፡፡ በመርሐ ግብሩ ላይ የኢንዱስትሪ ባለቤቶች፣ የደብረ ብርሃን ከተማ ስራ  ክህሎት አመራሮች፣ ተመራቂ ተማሪዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡

Notice image for  በደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና ደብረ ብርሃን ከተማ ስር የሚገኙ ኢንዱስትሪዎች በትብብር ለመስራት የሚያስችል የጋራ ውይይት ተካሄደ፡፡
Notice image for  በደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና ደብረ ብርሃን ከተማ ስር የሚገኙ ኢንዱስትሪዎች በትብብር ለመስራት የሚያስችል የጋራ ውይይት ተካሄደ፡፡
Notice image for  በደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና ደብረ ብርሃን ከተማ ስር የሚገኙ ኢንዱስትሪዎች በትብብር ለመስራት የሚያስችል የጋራ ውይይት ተካሄደ፡፡
Notice image for  በደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና ደብረ ብርሃን ከተማ ስር የሚገኙ ኢንዱስትሪዎች በትብብር ለመስራት የሚያስችል የጋራ ውይይት ተካሄደ፡፡
Notice image for  በደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና ደብረ ብርሃን ከተማ ስር የሚገኙ ኢንዱስትሪዎች በትብብር ለመስራት የሚያስችል የጋራ ውይይት ተካሄደ፡፡
Notice image for  በደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና ደብረ ብርሃን ከተማ ስር የሚገኙ ኢንዱስትሪዎች በትብብር ለመስራት የሚያስችል የጋራ ውይይት ተካሄደ፡፡
Notice image for  በደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና ደብረ ብርሃን ከተማ ስር የሚገኙ ኢንዱስትሪዎች በትብብር ለመስራት የሚያስችል የጋራ ውይይት ተካሄደ፡፡
Notice image for  በደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና ደብረ ብርሃን ከተማ ስር የሚገኙ ኢንዱስትሪዎች በትብብር ለመስራት የሚያስችል የጋራ ውይይት ተካሄደ፡፡
Notice image for  በደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና ደብረ ብርሃን ከተማ ስር የሚገኙ ኢንዱስትሪዎች በትብብር ለመስራት የሚያስችል የጋራ ውይይት ተካሄደ፡፡
Notice image for  በደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና ደብረ ብርሃን ከተማ ስር የሚገኙ ኢንዱስትሪዎች በትብብር ለመስራት የሚያስችል የጋራ ውይይት ተካሄደ፡፡
Notice image for  በደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና ደብረ ብርሃን ከተማ ስር የሚገኙ ኢንዱስትሪዎች በትብብር ለመስራት የሚያስችል የጋራ ውይይት ተካሄደ፡፡
Notice image for  በደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና ደብረ ብርሃን ከተማ ስር የሚገኙ ኢንዱስትሪዎች በትብብር ለመስራት የሚያስችል የጋራ ውይይት ተካሄደ፡፡
Notice image for  በደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና ደብረ ብርሃን ከተማ ስር የሚገኙ ኢንዱስትሪዎች በትብብር ለመስራት የሚያስችል የጋራ ውይይት ተካሄደ፡፡

ገበያ ተኮር በሆኑ የስራ ዘርፎች ወጣቶችን በአጫጭር ስልጠና በማብቃት ወደ ስራ እንዲገቡ እየተደረገ ነው

📅 2025-10-11 08:46:08

ገበያ ተኮር በሆኑ የስራ ዘርፎች ወጣቶችን በአጫጭር ስልጠና በማብቃት ወደ ስራ እንዲገቡ እየተደረገ ነው። በተያዘው በጀት ዓመትም ከ19ሺህ 2መቶ በላይ ወጣቶች ገበያ ተኮር በሆኑ አጫጭር ስልጠናዎችና ቴክኒካል ስልጠና ወደ ስራ ለማስገባት ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን በማንሳት ከአምሪፍ ሄልዝ አፍሪካ ጋር በመተባበር ለአንድ ወር በቧንቧ መስመር ዝርጋታና በኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ የሰለጠኑ 50 ሰልጣኞች ዛሬ በደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ተመርቀዋል። ከአምሪፍ ኸልዝ አፍሪካ ጋር ውል ገብቶ ወጣቶቹን ያሰለጠነው የደብረብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ባሻዬ በየነ በበኩላቸው ሰልጣኞች በተመረጡ የሙያ ዘርፎች ተገቢውን ተግባር ተኮር ስልጠና ወስደው 99ከመቶ የሚሆኑትም የሲኦሲ ምዘነውን በብቃት አጠናቀው የተመረቁ መሆናቸውን ገልፀዋል። የደብረብርሃን ከተማ ስራና ስልጠና መምሪያ ሀላፊ ወ/ሮ አይናለም ከፈለኝ እንዳሉት ስራ አጥ ዜጎችን በተለያዩ የስልጠና ዘርፎች የቴክኒካል እና የአጫጭር ስልጠናዎች አሰልጥኖ ወደ ስራ ለማስገባት ከመንግስት አቅም ባለፈ የተለያዩ ግብረሰናይ ድርጅቶች ጋር በመቀናጀት እየተሰራ ነው ብለዋል። የወሰድነው ስልጠና ተግባር ተኮር በመሆኑና ለስራ መነሻ የሚሆን ግብዓትም ከአምሪፍ በማግኘታችን በራስ አቅም ወደ ስራ ገብተን ከራሳችን ባለፈ ለሌሎችም የስራ እድል ለመፍጠር እንሰራለን ያሉት ደግሞ ያነጋገርናቸው ሰልጣኞች ናቸው። (የፖ/ሊ / ኮ/ ህዝብ ግንኑነት)

Notice image for  ገበያ ተኮር በሆኑ የስራ ዘርፎች ወጣቶችን በአጫጭር ስልጠና በማብቃት ወደ ስራ እንዲገቡ እየተደረገ ነው
Notice image for  ገበያ ተኮር በሆኑ የስራ ዘርፎች ወጣቶችን በአጫጭር ስልጠና በማብቃት ወደ ስራ እንዲገቡ እየተደረገ ነው
Notice image for  ገበያ ተኮር በሆኑ የስራ ዘርፎች ወጣቶችን በአጫጭር ስልጠና በማብቃት ወደ ስራ እንዲገቡ እየተደረገ ነው
Notice image for  ገበያ ተኮር በሆኑ የስራ ዘርፎች ወጣቶችን በአጫጭር ስልጠና በማብቃት ወደ ስራ እንዲገቡ እየተደረገ ነው
Notice image for  ገበያ ተኮር በሆኑ የስራ ዘርፎች ወጣቶችን በአጫጭር ስልጠና በማብቃት ወደ ስራ እንዲገቡ እየተደረገ ነው
Notice image for  ገበያ ተኮር በሆኑ የስራ ዘርፎች ወጣቶችን በአጫጭር ስልጠና በማብቃት ወደ ስራ እንዲገቡ እየተደረገ ነው
Notice image for  ገበያ ተኮር በሆኑ የስራ ዘርፎች ወጣቶችን በአጫጭር ስልጠና በማብቃት ወደ ስራ እንዲገቡ እየተደረገ ነው
Notice image for  ገበያ ተኮር በሆኑ የስራ ዘርፎች ወጣቶችን በአጫጭር ስልጠና በማብቃት ወደ ስራ እንዲገቡ እየተደረገ ነው
Notice image for  ገበያ ተኮር በሆኑ የስራ ዘርፎች ወጣቶችን በአጫጭር ስልጠና በማብቃት ወደ ስራ እንዲገቡ እየተደረገ ነው

የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ 2018 ዓ. ም የነባር መደበኛ ሰልጣኞችን የምዝገባ ቀን እና የስልጠና ቀን ይመለከታል;

📅 2025-09-24 05:12:43

Notice image for  የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ 2018 ዓ. ም የነባር መደበኛ ሰልጣኞችን የምዝገባ ቀን እና የስልጠና ቀን ይመለከታል;

የ 2017 ተመራቂ ተማሪዎችን ይመለከታል

📅 2025-08-12 11:04:07

Notice image for  የ 2017 ተመራቂ ተማሪዎችን ይመለከታል

አሻራ ምዝገባ ለምትፍልጉ

📅 2025-08-07 03:26:30

Notice image for  አሻራ ምዝገባ ለምትፍልጉ

የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮልጅ በ7 የሙያ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 6 መቶ 33 ተማሪዎች እያስመሰቀ ነው።

📅 2025-07-13 05:05:48

ደብረ ብርሃን፦ሐምሌ 6 ቀን 2017 ዓ.ም (ሰሸዞመኮ) የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮልጅ ለ27ኛ ዙር በ7 የሙያ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 6 መቶ 33 ተማሪዎች በአፄ ምኒልክ አዳራሽ እያስመሰቀ ይገኛል። ከሰልጣኞች መካከል 2 መቶ 80 የሚሆኑት ወንዶች ሲሆኑ 3 መቶ 53ቱ ደግሞ ሴቶች መሆናቸውንና ከደረጃ 2 እስከ ደረጃ 5 የሰለጠኑ መሆናቸውን የኮሌጁ ዋና ዲን የኮሌጁ ዲን አቶ ባሻዬ በየነ ገልጸዋል። የኮሌጁ ኃላፊ በማንፋከቸሪንግ ፣ በኤሌክትሪክሲቲ ፣ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፣ በጋርመንት ፣ በአውቶሞቲቭ ፣ በሆቴልና ቱሪዝም ፣ በሰርቬይንግ ያሰለጠናቸውን ሰልጣኞች በዛሬ እለት እያስመረቀ ነው ብለዋል አቶ ባሻዬ እንዳሉት ኮሌጁ ከተመሠረተበት ከ1989 ዓ.ም ጀምሮ በመደበኛው የትምህርት መርሐ-ግብር ብቻ ከ28 ሺህ በላይ ሰልጣኞችን አስመርቆ ወደ ሥራ ማሠመራቱን ገልጸዋል። ኮሌጁ በዚህ ዓመት ብቻ ለ27 ሺህ 7 መቶ ዜጎች የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪትን ጨምሮ በልዩ ልዩ የሙያ ዘርፎች አጫጭር ሥልጠና መስጠቱን አቶ ባሻዬ ተናግረዋል። በዛሬው እለት የእናንተ አንዱናየመጀመሪያው የሕይወታችሁ ምዕራፍ እንደመሆኑ ከሰለጠናችሁበት ሙያ በተጨማሪ አዳዲስ እውቀትና የሥራ ላይ ክህሎት እየጨመራችሁበት ሊያሠራችሁ በሚችል ቦታና ጊዜ እንድትጠቀሙበት እየተማመንኩ ችግሮችን ሁሉ በመጋፈጥ ተወዳዳሪ ሆናችሁ ያስተማራችሁን ማኅበረሰብ በሙያችሁ በፍጹም ቅንነት ፣ ታማኝነት እንድታገለግሉ አደራ እላለሁ ብለዋል። ጥሪ የተደረገላችሁም እንግዶች የተመራቂ ቤተሰቦች ፣ የሁላችሁም ፍሬዎች የሆኑትን የዛሬ ምሩቃንን በማስመረቅ እዚህ በመገኘታችሁ ታላቅ ደስታ ተሰምቶናል ሲሉ ተናግረዋል። የተመረቁ ሰልጣኞችን ከነገ ጀምሮ ተደራጅተው በተለያዩ ድርጅቶች ይሁን በግላቸው እንዲሰማሩ ከጎናቸው በመሆን አስፈላጊውን ድጋፍ እንድታደርጉላቸው እየጠየቅሁ ተመራቂዎችም መልካም የሥራ ዘመን እንዲሆንላችሁ ብለዋል።

Notice image for  የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮልጅ በ7 የሙያ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 6 መቶ 33 ተማሪዎች እያስመሰቀ ነው።
Notice image for  የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮልጅ በ7 የሙያ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 6 መቶ 33 ተማሪዎች እያስመሰቀ ነው።
Notice image for  የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮልጅ በ7 የሙያ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 6 መቶ 33 ተማሪዎች እያስመሰቀ ነው።
Notice image for  የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮልጅ በ7 የሙያ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 6 መቶ 33 ተማሪዎች እያስመሰቀ ነው።
Notice image for  የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮልጅ በ7 የሙያ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 6 መቶ 33 ተማሪዎች እያስመሰቀ ነው።
Notice image for  የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮልጅ በ7 የሙያ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 6 መቶ 33 ተማሪዎች እያስመሰቀ ነው።
Notice image for  የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮልጅ በ7 የሙያ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 6 መቶ 33 ተማሪዎች እያስመሰቀ ነው።
Notice image for  የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮልጅ በ7 የሙያ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 6 መቶ 33 ተማሪዎች እያስመሰቀ ነው።

ኮሌጃችን በኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የጥራት ሥራ አመራር ሥርአት ሰርተፊኬት ተሰጠው

📅 2025-06-05 02:17:38

ደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በዓለም አቀፍ የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ISO 9001-2015 (QMS) ተግባራዊ በማድረጉ የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የጥራት ሥራ አመራር ሥርአት ሰርተፊኬት ተሰጠው። ኮሌጁ የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ዓለም አቀፍ መመዘኛዎችን ማሟላቱን በተከናወነለት የኦዲት ሂደት ተገምግሞ ብቁ ሆኖ በመገኘቱ ሰርቲፊኬቱን ሊያገኝ ችሏል። የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ክብርት ኢ/ር መዓዛ አበራ ለኮሌጁ ዲን አቶ ባሻዬ በየነ ሰርቲፊኬቱን አስረክበዋል፡፡ በርክክብ ስነ ስርዓቱ ላይ ክብርት ኢ/ር መዓዛ አበራ የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል። እንኳን ደስ አለን ! እንኳን ደስ አላችሁ በዚህም ለኮሌጃችን አመራሮች፣ አሰልጣኞች፣ የአስተዳደር ሰራተኞች፣ ለኮሌጃችን ኳሊቲ ማኔጀርና ኢንተርናል ኳሊቲ ኦዲተር አባላት ይህን ስኬት ለማግኘት በምናደርገው ጥረት ሁሉ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ተሳትፎ ላደረጋችሁ በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ እንላለን። እንኳን ደስ አላችሁ

Notice image for  ኮሌጃችን በኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የጥራት ሥራ አመራር ሥርአት ሰርተፊኬት ተሰጠው

4ኛው ሀገርአቀፍ የክህሎት፣ የቴክኖሎጂና የጥናትና ምርምር ውድድር፣ የቴክኖሎጂ ኤግዚቢሽን እየተካሄደ ነው።

📅 2025-05-06 06:41:55

የኢፌዲሪ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ያዘጋጁት 4ኛው ሀገርአቀፍ የክህሎት፣ የቴክኖሎጂና የጥናትና ምርምር ውድድር፣ የቴክኖሎጂ ኤግዚቢሽን መካሄድ ጀመሯል። ውድድሩን በይፋ ያስጀመሩት የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር አቶ ተመስገን ጥሩነህ የዘመኑ ዐርበኝነት ድህነትና ኋላቀርነትን ቀርፎ ሁለንተናዊ ብልጽግናን ማረጋገጥ ነው ብለዋል። የክህሎት ልማት ለሀገራችን ዕድገት እና ብልፅግና ወሳኝ መሆኑን በማመን ባለፉት የለውጥ ዓመታት የሰራናቸው ስራዎች በፈጠራ የበሰሉ ብሩህ አዕምሮዎችን፣ የተፍታቱ እጆችን፣ በክህሎታቸው የበቁ ዜጎችን ለማፍራት አስችለዋል ብለዋል። ኢትዮጵያ ወራሪ ጠላትን መክተው ሉዓላዊነቷን ያስጠበቁ ጀግኖች ዐርበኞች እንደነበሯት ሁሉ ፤ ዛሬ ደግሞ የሙያንና የክህሎትን አቅም በመጠቀም ግብርናችንን የሚያዘምኑ፣ ለኢንዱስትሪ ዕድገት ወሳኝ መነሻ የሆኑ፣ የቱሪዝም ዘርፉን ውጤታማ የሚያደርጉ፣ ዲጂታላይዜሽንን የሚያፋጥኑ ብቁ ሙያተኞች አሏት በማለት ተናንረዋል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል በበኩላቸው ውድድሩ ከውድድር ባለፈ የቴክኒክና ሙያ ዘርፉ የቴክኖሎጂ ሽግግርን እውን የሚያደርግበት ሥርዓት ያበጀ ነው ብለዋል። ይህ ውድድር የዘመናችንን አድዋ መሐንዲሶችን የምናገኝበትና የምናፈራበት ፕሮግራም ነው ሲሉም ገልጽታል። ከውድድሩ በኋላ የተመረጡ የፈጠራ ውጤቶች ይበልጥ ዳብረው ወደ ብዝሀ ምርት የሚገቡበት ሁኔታ እንደተመቻቸ የገለጹት ክብርት ሚኒስትሯ በ3ኛው አገርአቀፍ ውድድር የተገኙ የፈጠራ ውጤቶች የዳበሩበት እና በርካታ ቴክኖሎጂስቶችን ማፍራት የተቻለበት እንደነበር አስታውሰዋል። ውድድሩ ከ250 በላይ ዜጎችን የሚያሳትፍ ሲሆን በውድድር አይነትና ጥራት ካለፉት ውድድሮች ተሻሽሎ መቅረቡን ክብርት ሚኒስትር ጨምረው ገልጸዋል። አራተኛውን የኢትዮ-ክህሎት ውድድር ልዩ የሚያደርገው በ22 ክህሎቶች ውድድር የሚደረግበትና ከ70 በላይ ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎች ለዕይታ የቀረቡበት መሆኑን ክብርት ሚኒስትር ገልጸዋል። ‘’ብሩህ አእምሮዎች፣ ለስራ የበቁ ዜጎች’’ በሚል መሪ ቃል ውድድሩ ለተከታታይ ስድስት ቀናት በኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ግቢ እየተደረገ ይገኛል።

Notice image for  4ኛው ሀገርአቀፍ የክህሎት፣ የቴክኖሎጂና የጥናትና ምርምር ውድድር፣ የቴክኖሎጂ  ኤግዚቢሽን እየተካሄደ ነው።

ደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በአጠቃላይ ውድድር 1ኛ ደረጃ በመሆን ጨርሳል።

📅 2025-05-05 05:37:51

የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በአጠቃላይ ውድድር 1ኛ ደረጃ በመሆን አሁንም ውድድሩን ጨርሳል። እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን !!! እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን !!!

Notice image for  ደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በአጠቃላይ ውድድር 1ኛ ደረጃ በመሆን ጨርሳል።

በክልል ሲካሄድ የሰነበተው የቴክኖሎጂ ክህሎት፤ የተግባር ጥናትና ምርምር ውድድር ላይ የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ውድድር 1ኛ ደረጃ በመሆን አጠናቀቀ

📅 2025-05-05 05:35:47

በክልል ሲካሄድ የሰነበተው የቴክኖሎጂ ክህሎት፤ የተግባር ጥናትና ምርምር ውድድር ላይ የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በአጠቃላይ ውድድር 1ኛ ደረጃ በመሆን አሁንም ውድድሩን ጨርሳል። እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን !!! እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን !!! "'ብሩህ አዕምሮዎች በክህሎት የበቁ ዜጎች '' በሚል መሪ መልዕክት የአብክመ ስራና ስልጠና ቢሮ አዘጋጅነት ከሚያዚያ 18_23/2017ዓ.ም ድረስ በአሠልጣኞች ፤ሠልጣኞች፤ኢንተርፕራይዞች እና ስራ ፈጣሪ ወጣቶች መካከል በኮምቦልቻ ከተማ ለ9ኛ ጊዜ በተካሄደው ክልላዊ የቴክኖሎጅ፣ የክህሎት፣ የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ፣ ኢንተርፕራይዞች የደረጃ ሽግግር እዉቅናና የንግድ ትርዒት ኤግዚቪሽን ውድድር ላይ የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ 57 ሜዳሊያዎችን በመሠብሠብ በአጠቃላይ ውጤት 1ኛ ደረጃ በመሆን ውድድሩን አጠናቋል። ውድድሩ የእርስ በእርስ የእውቀት የክህሎትና የአሰራር ልምዶችን ያካፈለ ከመሆኑ ባሻገር ችግሮችን በቴክኖሎጂ ፈጠራ እና በክህሎት ስራዎች ለመፍታት ወሳኝ መሆኑን ያሳየ ውድድር ተካሂዳል።ውድድሩም በየደረጃው ማለትም በኮሌጅ፣ ደረጃ ፣ በክላስተር ደረጀ ፣ በክልል አቀፍ ደረጃ ሲሆን ይሄን ብርቱና ጠንካራ ውድድር በማሸነፉ በሀገር አቀፍ ደረጃ የአሸናፊዎች አሸነፉ በአ.አበባ ከሚያዚያ 27 - ግንቦት 2/ 2017 ይካሄዳል። በውድድሩ በተገኘው ውጤት የተሳተፋችሁ ሁሉ ምስጋና እያቀረብን በድጋሚ እንኳን ደስ አለን::

Notice image for  በክልል  ሲካሄድ የሰነበተው የቴክኖሎጂ ክህሎት፤ የተግባር ጥናትና ምርምር ውድድር ላይ የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ውድድር 1ኛ ደረጃ በመሆን አጠናቀቀ

የደ/ብርሀን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በኢተርፕራይዝ የቀረበ የእህል መውቂያ ቴክኖሎጂ በውድድር ቦታ (ኮምፖልቻ) በክሬን ሲወርድ

📅 2025-04-26 04:00:16

በዘጠነኛው ክልል አቀፍ የቴክኖሎጂ የክህሎትና የተግባርዊ ጥናትና ምርምር ዉድድር የደ/ብርሀን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በኢተርፕራይዝ የቀረበ የእህል መውቂያ ቴክኖሎጂ በውድድር ቦታ (ኮምፖልቻ) በክሬን ሲወርድ

Notice image for  የደ/ብርሀን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በኢተርፕራይዝ የቀረበ የእህል መውቂያ ቴክኖሎጂ  በውድድር ቦታ (ኮምፖልቻ) በክሬን ሲወርድ

የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ምርጥ ተሞክሮ በኮሌጁ ዲን በአቶ ባሻዬ በየነ ቀረበ

📅 2025-02-18 00:57:14

የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሚገኙ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲኖች የፌደራል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና አመራሮች በተገኙበት በቢሾፍቱ ከተማ የካቲት 9/2017ዓ.ም በተደረገው ስብሰባ ላይ የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ምርጥ ተሞክሮ በኮሌጁ ዲን በአቶ ባሻዬ በየነ ቀርቧል።በቀረበውም ተሞክሮ ውይይት ተደርጓል

Notice image for  የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ምርጥ ተሞክሮ በኮሌጁ ዲን በአቶ ባሻዬ በየነ ቀረበ
Notice image for  የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ምርጥ ተሞክሮ በኮሌጁ ዲን በአቶ ባሻዬ በየነ ቀረበ
Notice image for  የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ምርጥ ተሞክሮ በኮሌጁ ዲን በአቶ ባሻዬ በየነ ቀረበ
Notice image for  የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ምርጥ ተሞክሮ በኮሌጁ ዲን በአቶ ባሻዬ በየነ ቀረበ

የደብረ ብርሃን ፖሊ ትክኒክ ኮሌጅ የ ISO ትግበራላይ ነዉ

📅 2025-01-29 02:19:26

ISO 9001:2015 ማለት ምን ማለት ነው? ISO 9001:2015 የሚለው የአለም አቀፍ ደረጃ ለጥራት አስተዳደር ስርዓት (Quality Management System - QMS) የሚያቀርብ መመሪያ ነው። ይህ ደረጃ ድርጅቶች ምርቶቻቸውን እና አገልግሎቶቻቸውን በተጠበቀ መልኩ ለደንበኞች እንዲያቀርቡ የሚያስችል አግባብነት ያለው ስርዓት እንዲመሰርቱ ይረዳቸዋል። የISO 9001:2015 ደረጃ በማንኛውም የኢንዱስትሪ ዘርፍ የሚሰራ ድርጅት ሊተገበር ይችላል። ISO 9001:2015 መተግበር ለምን ይጠቅማል? ISO 9001:2015 መተግበር ለድርጅቶች ብዙ ጥቅሞችን ያስገኛል። ከነዚህም መካከል ዋነኛዎቹ የሚከተሉት ናቸው። የጥራት ማሻሻያ ISO 9001:2015 የጥራት አስተዳደር ስርዓትን በመተግበር ድርጅቶች ምርቶቻቸውን እና አገልግሎቶቻቸውን በተጠበቀ መልኩ ለደንበኞች እንዲያቀርቡ ይረዳቸዋል። ይህም የምርት ጥራትን ያሻሽላል እና የደንበኞችን እርካታ ያሳድጋል። የደንበኞች እርካታ ማሳደግ ይህ ደረጃ የደንበኞችን ፍላጎቶች እና የሚጠበቁትን ውጤት ለመረዳት እና ለማሟላት የሚያስችል ስርዓት ያቀርባል። ይህም የደንበኞችን እርካታ ያሳድጋል እና የድርጅቱን ምርት እና አገልግሎት በገበያ ውስጥ የማረጋገጥ አቅም ይጨምራል። የውስጥ ሂደቶች ማሻሻያ ISO 9001:2015 የውስጥ ሂደቶችን ለማሻሻል እና ለማመቻቸት የሚያስችል መርሆዎችን ያቀርባል። ይህም የድርጅቱን ውጤታማነት ያሳድጋል እና ወጪዎችን ይቀንሳል። የደንበኞች እምነት ማሳደግ ISO 9001:2015 የሚለው የአለም አቀፍ ደረጃ የተረጋገጠ የጥራት አስተዳደር ስርዓት እንዳለው የሚያሳይ ምልክት ነው። ይህም የደንበኞችን እምነት ያሳድጋል እና የድርጅቱን ተወዳዳሪነት በገበያ ውስጥ ያሻሽላል። የአለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ISO 9001:2015 የአለም አቀፍ ደረጃ በመሆኑ ድርጅቶች በዓለም አቀፍ ደረጃ ላይ እንዲወዳደሩ ያስችላቸዋል። ይህም በተለይም ለምርቶቻቸውን እና አገልግሎቶቻቸውን ወደ ውጭ ለመላክ የሚፈልጉ ድርጅቶች በጣም ጠቃሚ ነው። የህግ እና ደንብ መሟላት ISO 9001:2015 የሚያስፈልጉትን ህጎች እና ደንቦች ለመሟላት የሚያስችል ስርዓት ያቀርባል። ይህም ድርጅቶች ከህግ ጋር የሚጋጩ ችግሮችን ለማስወገድ ይረዳቸዋል። የሰራተኞች ተሳትፎ ማሳደግ ISO 9001:2015 የሰራተኞችን ተሳትፎ እና ተጠያቂነት ለማሳደግ የሚያስችል ስርዓት ያቀርባል። ይህም የሰራተኞችን ምክንያታዊነት እና የሥራ እርካታ ያሳድጋል። ማጠቃለያ ISO 9001:2015 መተግበር ለድርጅቶች በጥራት አስተዳደር፣ የደንበኞች እርካታ፣ የውስጥ ሂደቶች ማሻሻያ እና የአለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ላይ ብዙ ጥቅሞችን ያስገኛል። ይህ ደረጃ ድርጅቶች በተደጋጋሚ ራሳቸውን ለማሻሻል እና በገበያ ውስጥ የተሻለ ቦታ ለማግኘት ይረዳቸዋል።

Notice image for  የደብረ ብርሃን ፖሊ ትክኒክ ኮሌጅ የ ISO ትግበራላይ ነዉ

የደብረ ብርሃን ፖሊ ትክኒክ ኮሌጅ የ ISO ሳምንት በማክበር ላይ ይገኛል

📅 2025-01-29 02:16:01

Notice image for  የደብረ ብርሃን ፖሊ ትክኒክ ኮሌጅ የ ISO ሳምንት በማክበር ላይ ይገኛል

የአማራ ክልል ስራና ስልጠና ቢሮ የደብረብርሃን ከተማ እና የሰሜን ሸዋ የፖሊ ቴክኒክ እና የኮሌጆች የ4 ወራት አፈፃጸም ግምገማ እያካሄደ ነው

📅 2024-11-15 05:06:44

«በበጀት ዓመቱ ለ1 ነጥብ 2 ሚሊየን ዜጎች የስራ ዕድል ለመፍጠር እየተሰራ ነው» - አማረ አለሙ ደብረብርሃን ፡ ኅዳር 4/2017ዓ.ም የአማራ ክልል ስራና ስልጠና ቢሮ የደብረብርሃን ከተማ እና የሰሜን ሸዋ የፖሊ ቴክኒክ እና የኮሌጆች የ4 ወራት አፈፃጸም ግምገማ እያካሄደ ነው የአማራ ክልል ስራና ስልጠና ቢሮ ምክትል ኃላፊና የትምህርትና ስልጠና ዘርፍ አስተባባሪ አቶ አማረ አለሙ ፕሮግራሙን ሲከፍቱ እንደተናገሩት የመድረኩ ዓላማ የሩብ ዓመቱን አፈፃጸም በመገምገም የቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ መሆኑን አስረድተዋል። ኮሌጆች በተሰጣቸው የ100 ቀናት ዕቅድ መሠረት አፈፃጸሙን በመገምገም ጥንካሬዎችን ለማስቀጠልና እጥረቶችን ለማስተካከል የውይይት መድረኩ መመቻቸቱን አንስተዋል። በተለይም ከመደበኛ ስልጠና በዘለለ ክህሎት መር የስራ ዕድል ፈጠራ ስልጠና በመስጠት ዜጎች ሰርተው ራሳቸውን እንዲለውጡ ኮሌጆች እና የዘርፉ ተዋናዮች ብዙ መስራት እንዳለባቸው አመልክተዋል። በመንግስት ድጋፍ ተደርጎላቸው ዘላቂ እና ወደ መካከለኛ ባለሃብት የሚሸጋገሩ ወጣቶችንና ኢንተርፕራይዞችን ለማፍራት አንድ የትኩረት አቅጣጫ ሆኖ እየተሰራ እንደሚገኝም አብራርተዋል። ከዚህ በተጨማሪ በዲጅታላይዜሽን ዘርፍ ኮሌጆች የማስፋፋት ስራዎችን እንዴት እየተገበሩ እንደሆነና በሌሎችም ተግባራት ላይ ውይይቱ የሚካሄድ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በዚሁ መሠረት በ2017 ዓ.ም 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ለሚሆኑ ዜጎቸ የስራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። በተያያዘም በመደበኛ ትምህርትና ስልጠና 198ሺ ፣ በኢንተርፕራይዝ ስልጠና 958ሺ፣ በቴክኒካል ስልጠና 456ሺ ወጣቶችን ለማሰልጠን መታቀዱን አመልክተዋል። የደብረብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዋና ዲን አቶ ባሻየ በየነ የኮሌጃቸውን ዕቅድ አፈፃጸም አቅርበዋል። በግምገማ መድረኩ የደብረ ብርሃን ከተማ እና የሰሜን ሸዋ ዞን ፖሊና ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች፣ የስራና ስልጠና የስራ ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።

Notice image for   የአማራ ክልል ስራና ስልጠና ቢሮ የደብረብርሃን ከተማ እና የሰሜን ሸዋ የፖሊ ቴክኒክ እና  የኮሌጆች የ4 ወራት አፈፃጸም ግምገማ እያካሄደ ነው
Notice image for   የአማራ ክልል ስራና ስልጠና ቢሮ የደብረብርሃን ከተማ እና የሰሜን ሸዋ የፖሊ ቴክኒክ እና  የኮሌጆች የ4 ወራት አፈፃጸም ግምገማ እያካሄደ ነው
Notice image for   የአማራ ክልል ስራና ስልጠና ቢሮ የደብረብርሃን ከተማ እና የሰሜን ሸዋ የፖሊ ቴክኒክ እና  የኮሌጆች የ4 ወራት አፈፃጸም ግምገማ እያካሄደ ነው
Notice image for   የአማራ ክልል ስራና ስልጠና ቢሮ የደብረብርሃን ከተማ እና የሰሜን ሸዋ የፖሊ ቴክኒክ እና  የኮሌጆች የ4 ወራት አፈፃጸም ግምገማ እያካሄደ ነው
Notice image for   የአማራ ክልል ስራና ስልጠና ቢሮ የደብረብርሃን ከተማ እና የሰሜን ሸዋ የፖሊ ቴክኒክ እና  የኮሌጆች የ4 ወራት አፈፃጸም ግምገማ እያካሄደ ነው
Notice image for   የአማራ ክልል ስራና ስልጠና ቢሮ የደብረብርሃን ከተማ እና የሰሜን ሸዋ የፖሊ ቴክኒክ እና  የኮሌጆች የ4 ወራት አፈፃጸም ግምገማ እያካሄደ ነው
Notice image for   የአማራ ክልል ስራና ስልጠና ቢሮ የደብረብርሃን ከተማ እና የሰሜን ሸዋ የፖሊ ቴክኒክ እና  የኮሌጆች የ4 ወራት አፈፃጸም ግምገማ እያካሄደ ነው
Notice image for   የአማራ ክልል ስራና ስልጠና ቢሮ የደብረብርሃን ከተማ እና የሰሜን ሸዋ የፖሊ ቴክኒክ እና  የኮሌጆች የ4 ወራት አፈፃጸም ግምገማ እያካሄደ ነው

የአብክመ ስራና ስልጠና ቢሮ የ2017ዓ.ም በጀት አመት የ1ኛ ሩብ ዓመት አፈፃፀም የሱፐርቪዥን ቡድን ግምገማ እያደረጉ ይገኛል።

📅 2024-11-12 21:14:11

የአብክመ ስራና ስልጠና ቢሮ የ2017ዓ.ም በጀት አመት የ1ኛ ሩብ ዓመት አፈፃፀም የሱፐርቪዥን ቡድን በደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ውስጥ በተዘጋጀው ቼክ ሊስት መሠረት ግምገማ እያደረጉ ይገኛል።

Notice image for  የአብክመ ስራና ስልጠና ቢሮ የ2017ዓ.ም በጀት አመት የ1ኛ ሩብ ዓመት አፈፃፀም የሱፐርቪዥን ቡድን ግምገማ እያደረጉ ይገኛል።
Notice image for  የአብክመ ስራና ስልጠና ቢሮ የ2017ዓ.ም በጀት አመት የ1ኛ ሩብ ዓመት አፈፃፀም የሱፐርቪዥን ቡድን ግምገማ እያደረጉ ይገኛል።
Notice image for  የአብክመ ስራና ስልጠና ቢሮ የ2017ዓ.ም በጀት አመት የ1ኛ ሩብ ዓመት አፈፃፀም የሱፐርቪዥን ቡድን ግምገማ እያደረጉ ይገኛል።
Notice image for  የአብክመ ስራና ስልጠና ቢሮ የ2017ዓ.ም በጀት አመት የ1ኛ ሩብ ዓመት አፈፃፀም የሱፐርቪዥን ቡድን ግምገማ እያደረጉ ይገኛል።

ኮሌጁ በቀጣይ 3 እና 4 ወራት ውስጥ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሚያደርገውን የISO ሰርተፍኬት ለማግኘት እየሰራ መሆኑን አስታወቀ

📅 2024-11-04 16:48:29

ደብረብርሃን፣ጥቅምት 22/2017(ደብኮ):- የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በቀጣይ 3 እና 4 ወራት ውስጥ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሚያደርገውን የISO 9001/2015 ሰርተፍኬት ለማግኘት ለመምህራን እና ሠራተኞች ስልጠና እየሰጠ መሆኑን አስታውቋል። የኮሌጁ ዲን አቶ ባሻዬ በየነ እንደገለጹት ኮሌጃቸው አዳዲስ እሳቤዎችን መነሻ በማድረግ ለኢንተርፕራይዞች፣ ለደብረብርሃንና ለሰሜን ሸዋ አካባቢዎች አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ አንስተዋል። ለተሽከርካሪዎች የቦሎ ምርመራ ፣ለሾፌሮች ስልጠና በመስጠት በአንድ በኩል ለህብረተሰቡ ተስማሚ አገልግሎት እንዲሰጡ፣ በሌላ በኩል ደረጃቸውን እንዲያሳድጉ ተቋማቸው እየሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል። በተለይም በክልሉ ከፍተኛ ሰልጣኝ ተቀብሎ በጥራት በማሰልጠን ተወዳዳሪነቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን አስታውቀዋል። የኮሌጁን ተወዳዳሪነት በሀገር አቀፍ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማሳደግ በISO 9001/2015 የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ዙሪያ 3 መቶ ለሚሆኑ መምህራን እና ሠራተኞች ስልጠና እየሰጡ መሆኑን አቶ ባሻዬ አመልክተዋል። ስልጠናው የዓለም አቀፍ ደረጃ መስፈርት ያሟላ እንዲሆን በISO የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት እና በISO ኦዲቲንግ ዙሪያ ለ5 አሰልጣኝ መምህራን በኢትዮጵያ ጥራትና ደረጃዎች ባለስልጣን ስልጠና መውሰዳቸውን አስረድተዋል። ኮሌጃቸው ከስልጠና በኃላ በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ትግበራ እንደሚገባና በቀጣይ 3 እና 4 ወራት ውስጥ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሚያደርገውን የISO ሰርተፍኬት ለማግኘት እየሰራ መሆኑን አስታወቀዋል። በዚህም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪና ተቀባይነት ያላቸው ሰልጣኞችን ለማፍራት የኮሌጁ የስራ ኃላፊዎች፣ መምህራን እና ሠራተኞች ከፍተኛ መነሳሳት ማሳየታቸውን እና መግባባት ላይ መድረሳቸውን ዲኑ አብራርተዋል። የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የጥራት ማረጋገጥ ኃላፊ ኢንስትራክተር ተስፋዬ አያሌው በበኩላቸው እንደገለጹት ISO ብዙ ጊዜ ለትልልቅ ኩባንያ እና ለምርት ተቋም ብቻ ሳይሆን ከትንሽ እስከ ትልቅ ተቋም የሚያገለግል የስራ አመራር ስርዓት የሚዘረጋ መሆኑን አመልክተዋል። ተቋማቸው ISO 9001/2015 ወይም የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ለመተግበር ቅድመ ዝግጅት ማጠናቀቁን አስታውቀዋል። ISO ስራ በቀላሉ እንዲሰራ የሚያደርግ ፣ምርታማነትን የሚጨምር፣ አገልግሎት አሰጣጥን በማቀላጠፍ የደንበኛ እርካታን የሚያሳድግ፣ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቁመዋል። በዚሁ መሠረት ተቋማቸው ከዚህ በፊት የሚታወቅበትን አሻሽሎ ISOን በመተግበር የሰልጣኞችን ፣የኢንተርፕራይዞችን፣ የአካባቢውን ማህበረሰብ እና የመንግስትን እርካታ በማረጋገጥ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ለመሆን እንደሚሰራ አመልክተዋል።

Notice image for  ኮሌጁ በቀጣይ 3 እና 4 ወራት ውስጥ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሚያደርገውን የISO ሰርተፍኬት ለማግኘት እየሰራ መሆኑን አስታወቀ
Notice image for  ኮሌጁ በቀጣይ 3 እና 4 ወራት ውስጥ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሚያደርገውን የISO ሰርተፍኬት ለማግኘት እየሰራ መሆኑን አስታወቀ
Notice image for  ኮሌጁ በቀጣይ 3 እና 4 ወራት ውስጥ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሚያደርገውን የISO ሰርተፍኬት ለማግኘት እየሰራ መሆኑን አስታወቀ
Notice image for  ኮሌጁ በቀጣይ 3 እና 4 ወራት ውስጥ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሚያደርገውን የISO ሰርተፍኬት ለማግኘት እየሰራ መሆኑን አስታወቀ
Notice image for  ኮሌጁ በቀጣይ 3 እና 4 ወራት ውስጥ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሚያደርገውን የISO ሰርተፍኬት ለማግኘት እየሰራ መሆኑን አስታወቀ
Notice image for  ኮሌጁ በቀጣይ 3 እና 4 ወራት ውስጥ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሚያደርገውን የISO ሰርተፍኬት ለማግኘት እየሰራ መሆኑን አስታወቀ
Notice image for  ኮሌጁ በቀጣይ 3 እና 4 ወራት ውስጥ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሚያደርገውን የISO ሰርተፍኬት ለማግኘት እየሰራ መሆኑን አስታወቀ
Notice image for  ኮሌጁ በቀጣይ 3 እና 4 ወራት ውስጥ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሚያደርገውን የISO ሰርተፍኬት ለማግኘት እየሰራ መሆኑን አስታወቀ
Notice image for  ኮሌጁ በቀጣይ 3 እና 4 ወራት ውስጥ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሚያደርገውን የISO ሰርተፍኬት ለማግኘት እየሰራ መሆኑን አስታወቀ

የ 2017 ዓ.ም የአዲስ ተማሪዎች ቅበላን ይመለከታል…

📅 2024-10-25 00:29:35

Notice image for  የ 2017 ዓ.ም የአዲስ ተማሪዎች ቅበላን ይመለከታል…

አዲስ ሰልጣኝ ቅበላ የምናደርግባቸዉ ሙያዎች የአካባቢዉን የመልማት ፀጋ ተለይቶ በተፈቀዱልን 5 ዘርፎች

📅 2024-09-24 12:45:19

ለ2017 አዲስ ለስልጠና ፈላጊዎች በሙሉ የደብረብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እንኳን ለ2017 ዓ.ም የስልጠና ዘመን አደረሳችሁ እያለ አዲስ ሰልጣኝ ቅበላ የምናደርግባቸዉ ሙያዎች የአካባቢዉን የመልማት ፀጋ ተለይቶ በተፈቀዱልን 5 ዘርፎች ብቻ (Distinctive area of competency /DAC) መሰረት 12ኛ ክፍል አጠናቃችሁ በተለያየ የዉጤት ይዛችሁ ስልጠና ፈላጊዎች ከ ደረጃ 1 እስከ ደረጃ 5 የምናሰለጥን መሆኑን አዉቃችሁ ስልጠና ፈላጊዎች እንደየ ዉጤታችሁ ለየደረጃችሁ የመቁረጫ ነጥብ ይፋ እስኪሆን ድረስ ደብረንርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የምንሰጣችዉን የስልጠና አይነቶች እና ደረጃ እንደሚከተለዉ እያሳወቅን የምዝገባ ቀኑን እና መስፈርቱን በቅርብ ስለምናሳዉቃችሁ ቅድመ ዝግጅት እያደረጋችሁ እንድትጠብቁን በአክብሮት እናሳዉቃለን ፡፡ ስልጠና የምንሰጥባቸዉ ሙያዎች ደረጃዎችን ከስር ይመልከቱ

Notice image for  አዲስ ሰልጣኝ ቅበላ የምናደርግባቸዉ ሙያዎች የአካባቢዉን የመልማት ፀጋ ተለይቶ በተፈቀዱልን 5 ዘርፎች

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የስራና ስልጠና ቢሮ የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ባመጣዉ አመርቂ ዉጤት የእዉቅና የምስክር ወረቀት አበረከተ

📅 2024-08-14 18:44:58

የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የእዉቅና የምስክር ወረቀት

Notice image for  በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ  መንግስት የስራና ስልጠና ቢሮ  የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ባመጣዉ አመርቂ ዉጤት የእዉቅና የምስክር ወረቀት አበረከተ
Notice image for  በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ  መንግስት የስራና ስልጠና ቢሮ  የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ባመጣዉ አመርቂ ዉጤት የእዉቅና የምስክር ወረቀት አበረከተ

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የስራና ስልጠና ቢሮ የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ባመጣዉ አመርቂ ዉጤት የእዉቅና የምስክር ወረቀት አበረከተ

📅 2024-08-14 18:43:24

የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ባሻዬ በየነ የእዉቅና የምስክር ወረቀት ሲቀበሉ

Notice image for  በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ  መንግስት የስራና ስልጠና ቢሮ  የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ባመጣዉ አመርቂ ዉጤት የእዉቅና የምስክር ወረቀት አበረከተ

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የስራና ስልጠና ቢሮ የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ባመጣዉ አመርቂ ዉጤት የእዉቅና የምስክር ወረቀት አበረከተ

📅 2024-08-14 18:32:22

እንኳን ደስ አላችሁ !!! የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በአብክመ የስራና ስልጠና ቢሮ ባዘጋጀዉ በ2016 በጀት ዓ.ም በአደረገዉ የእቅድ አፈፃፀም ግምገማ በ 1ኛ ደረጃ በመዉጣት ይህ እዉቅና እና የምስጋና የምስክር ወረቀት ተሰቶታል እንዲሁም የላብቶብ ተሸላሚ መሆን ችለናል የኮሌጁ መምህራን እና ሰራተኞች በሙሉ በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ እንላለን ፡፡ የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ነሐሴ 8/2016

Notice image for  በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ  መንግስት የስራና ስልጠና ቢሮ  የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ባመጣዉ አመርቂ ዉጤት የእዉቅና የምስክር ወረቀት አበረከተ
Notice image for  በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ  መንግስት የስራና ስልጠና ቢሮ  የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ባመጣዉ አመርቂ ዉጤት የእዉቅና የምስክር ወረቀት አበረከተ
Notice image for  በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ  መንግስት የስራና ስልጠና ቢሮ  የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ባመጣዉ አመርቂ ዉጤት የእዉቅና የምስክር ወረቀት አበረከተ
Notice image for  በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ  መንግስት የስራና ስልጠና ቢሮ  የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ባመጣዉ አመርቂ ዉጤት የእዉቅና የምስክር ወረቀት አበረከተ

Guest of honor Ato Bedilu mayor of Debre Birhan Regio Politian City Administration place message D/B Polytechnic Graduate

📅 2024-07-15 18:59:24

Guest of honor Ato Bedilu mayor of Debre Birhan Regio Politian City Administration place message D/B Polytechnic Graduate

Notice image for  Guest of honor Ato Bedilu mayor of Debre Birhan Regio Politian City Administration place message D/B Polytechnic Graduate

DBPTC Leaders at Graduation Hall

📅 2024-07-15 18:51:50

DBPTC Leaders at Graduation Hall

Notice image for  DBPTC Leaders at Graduation Hall

High Score Achiever

📅 2024-07-15 18:29:09

High Point Achiever

Notice image for  High Score Achiever

Debre Polytechnic Dean

📅 2024-07-15 17:37:54

Debre Polytechnic Dean Ato Bashaye Beyene place his statement during Graduation

Notice image for  Debre Polytechnic Dean

Graduation

📅 2024-07-15 17:34:31

Notice image for  Graduation
Notice image for  Graduation
Notice image for  Graduation
Notice image for  Graduation
Notice image for  Graduation
Notice image for  Graduation
Notice image for  Graduation

Our Great Achievement

📅 2024-07-15 16:58:35

Debre Birhan Polytechnic College got reward due to high achievement compared across the country.

Notice image for  Our Great Achievement
Notice image for  Our Great Achievement
Notice image for  Our Great Achievement

የአይቲ ሰልጣኞች ተቋማዊ ምዘና ወሰዱ

📅 2024-07-13 19:19:29

በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ት/ም ክፍል ሰልጣኞች ተቋማዊ ምዘና ወሰዱ

Notice image for  የአይቲ ሰልጣኞች ተቋማዊ ምዘና ወሰዱ

በተለያዩ ሙያ የሰልጠኑ ሰልጣኞች ተቋማዊ ምዘና ወሰዱ

📅 2024-07-13 19:17:23

በኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ ት/ም ክፍል ያሉ ሰልጣኞች ተቋማዊ ምዘና ወሰዱ

Notice image for  በተለያዩ ሙያ የሰልጠኑ ሰልጣኞች ተቋማዊ ምዘና ወሰዱ

የኮሌጃችን ስኬት

📅 2024-07-13 19:02:24

በፌደራል ደረጃ በተካሄደው አጠቃላይ የቴክንክና ሙያ ኮሌጆች ውድድር #የደብረብርሃን_ፖሊቴክንክ_ኮሌጅ አንደኛ ደረጃ ወጥቷል። የላቀ አፈፃፀም ያስመዘገቡ ሦስት የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች እውቅና ተሰጣቸው በክህሎት ልማት ዘርፉ ተግባራዊ የተደረገውን ሪፎርም ተከትሎ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ከማሰልጠን በላይ ተልዕኮ ወስደው ወደ ተግባር ገብተዋል፡፡ በሪፎርሙ ተቋማቱ ኢንተርኘሪነራል እሳቤን ተላብሰው ሥራ ፈላጊ ዜጎች የሥራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከመደበኛው ሥልጠና ጎን ለጎን አጫጭር ስልጠናዎችን በመስጠት፣ ኢንተርፕራዞችን በማደራጀት፣ ወደ ሥራ ለገቡ ኢንተርፕራይዞችን ቀጣይነት ያለው ሙያዊ ድጋፍ በማድረግ የማሰልጠኛ ተቋም ብቻ ሳይሆን ለሥራ ዕድል ፈጠራው የዕድል በሮችም ጭምር ሆነው የሚያገለግሉበት አቅጣጫ ተቀምጦ ተግባራዊ በመደረግ ላይ ይገኛል፡፡ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረትም የተቋማትን የ2015 በጀት ዓመት የሥራ አፈፃፀም መነሻ በማድረግ ሦስት ምርጥ ተቋማት በመጀመሪያው የአፍሪካ የሥራ ጉባኤ ላይ እውቅና ተሰጥቷቸዋል፡፡ በዚህም መሰረት የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አንደኛ፣ አዳማ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሁለተኛ እንዲሁም የሀዋሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሦስተኛ በመሆን በሀገር አቀፍ ደረጃ በበጀት ዓመቱ የላቀ አፈፃፀም ያስመዘገቡ በመሆናቸው እውቅና ተሰጥቷቸዋል፡፡

Notice image for  የኮሌጃችን ስኬት

የትራንስፖርት ቴክኒሽያን ብቃት ማረጋገጫ የአሽከርካሪዎች የመግቢያ ፈተና

📅 2024-07-13 18:20:58

ከሁለተ አስርተ አመታተ በላይ ህብረተሰባችንን ቅንነት እና ብቃት ባላቸዉ አሰልጣኞቻችን ብዙዎችን ባለሙያ ማድረጋችን ይታወቃል ፡፡\r\n አሁን ደግሞ ከዚህ በፊት ቃል በገባነዉ መሰረት የትራንስፖርት ቴክኒሽያን ብቃት ማረጋገጫ ተቐማችን በዚህ መልኩ በቀን 09/08/2016 አሽከርካሪዎችን የመግቢያ ፈተና በመስጠት ስልጠና በይፋ መጀመራችንን እየገልፅን ከዚህ በኃላ ማንኛዉም አሽከርካሪ ስልጠናዉን በመዉሰድ የትራንስፖርት ባለቤት መሆን እንደምትችሉ በዚሁ አጋጣሚ ለመግለጽ እንወዳለን ፡፡ \r\n \r\n የደ/ብርሀን ፖሊ/ቴ/ኮሌጅ የተሽከርካሪዎች ቴክኒሽያን ብቃት ማረጋገጫ ተቐም !!!

Notice image for  የትራንስፖርት ቴክኒሽያን ብቃት ማረጋገጫ  የአሽከርካሪዎች  የመግቢያ ፈተና

የተሽከርካሪ ምርምራ መስጠት ተጀመረ

📅 2024-07-13 15:42:54

ኮሊጃችን የተሽከርካሪ ምርምራ መስጠት መጀመሩን ይፋ አደርገ

Notice image for  የተሽከርካሪ ምርምራ መስጠት ተጀመረ

የትራንስፖርት ቴክንሽያን ብቃት ማረጋገጫ(አፕሩቫል)

📅 2024-07-13 15:36:17

ኮሌጃችን የትራንስፖርት ቴክንሽያን ብቃት ማረጋገጫ(አፕሩቫል) ለመስጠት ዝግጅቱን አጠናቀቀ

Notice image for  የትራንስፖርት ቴክንሽያን ብቃት ማረጋገጫ(አፕሩቫል)

Sustainable Employment through Entrepreneurship & Enterprise Development (Seed) Project Training

📅 2024-07-13 15:26:10

የደብረ ብርሀን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ Sustainable Employment through Entrepreneurship & Enterprise Development (Seed) Project ላይ ለደብረ ብርሀን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አመራሮች፣ ዲፖርትመንት ተጠሪዎች፣ አጠቃላይ መምህራን እና የአስተዳደር ሠራተኞች እንዲሁም ከደ/ብርሀን ሪጅዮ ፖሊታን ስራና ስልጠና መምሪያ የስራ እድል ፈጠራ ቡድን መሪና የስልጠና ቡድን መሪዎች ባሉበት በ08/06/2016ዓ.ም ለአንድ ቀን በአቶ ባሻዬ በየነ በደ/ብርሀን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን በሆኑት ስልጠና የተሠጠ ሲሆን የኮሌጁ ማህበረሰብም ፕሮጀክቱ የሚጠበቅበትን ለማበርከት ዝግጁ መሆንን አረጋግጠዋል

Notice image for  Sustainable Employment through Entrepreneurship & Enterprise Development (Seed) Project Training
29534 views