📅 2026-07-24 07:50:04(20 days ago)
ደብረ ብርሃን፦ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ላለፉት 5 ተከታታይ ዓመታት በአማራ ክልል በአንደኛ ደረጃነት የሚገኘው ደብረ ብርሃን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ፣ ከራሱ አልፎ ለሌሎች ተቋማት የልህቀት ማዕከል በመሆን አቅም ሊፈጥር እንደሚገባ ተገልጿል።
📅 2026-07-24 07:46:19(20 days ago)
ደብረ ብርሃን፦ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ላለፉት 5 ተከታታይ ዓመታት በአማራ ክልል በአንደኛ ደረጃነት የሚገኘው ደብረ ብርሃን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ፣ ከራሱ አልፎ ለሌሎች ተቋማት የልህቀት ማዕከል በመሆን አቅም ሊፈጥር እንደሚገባ ተገልጿል።
📅 2026-07-19 15:48:21(25 days ago)
ደብረ ብርሃን፤ሀምሌ 12/2018(ደብመኮ):-አንጋፋው የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በመደበኛው እና በማታው መርሐ ግብር በ5 የትምህርት መስኮች ከደረጃ 2 እስከ ደረጃ 5 ያሰለጠናቸውን 1ሺህ 196 አሰልጣኞች አስመርቋል። በመርሐ ግብሩ ላይ የደብረ ብርሃን ከተማ ተቀዳሚ ከንቲባ የተከበሩ በድሉ ውብሸት፣የደብረ ብርሃን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዋና ዲን አቶ ባሻየ በየነን ጨምሮ የደብረ ብርሃን ከተማና የሰሜን ሸዋ ዞን የሥራ ኃላፊዎች፣የተመራቂ ቤተሰቦች እና ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል። የደብረ ብርሃን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ባሻየ በየነ እንደገለጹት፣ኮሌጁ በ2018 በጀት ዓመት በክልሉ ከሚገኙ ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች መካከል ከፍተኛ የሰልጣኞች ቁጥር በማሰልጠን፣ በማስመረቅ እንዲሁም አዳዲስ እሳቤዎችን ተግባራዊ በማድረግ ለአምስት ተከታታይ ዓመታት አንደኛ ደረጃን በመያዝ የላቀ አፈጻጸም ማስመዝገቡን አስታውቀዋል። ኮሌጁ ያገኘውን ተከታታይ አሸናፊነት ለማስቀጠል የበላይ አመራሮች፣ አስተማሪዎች፣ ሠራተኞች እና አጋር አካላት ላበረከቱት አስተዋጽዖ ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን፣የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር፣ አጫጭር ስልጠናዎች፣ የኮኦፕሬቲቭ ስልጠና፣ የማሽን ጥገና እና የካይዘን (Kaizen) አሰራርን በስፋት ተግባራዊ ማድረጉን አንስተዋል። በ2018 ዓ.ም ኮሌጁ በ7 የሙያ መስኮች ከደረጃ 2 እስከ ደረጃ 5 ያሰለጠናቸውን 1 ሺህ 1 መቶ 96 ሰልጣኞች በድምቀት ማስመረቁን ገልጸው፣ከተመራቂዎቹ መካከል 6 መቶ 70 የሚሆኑት ወንዶች ሲሆኑ፣ 5 መቶ 26ቱ ደግሞ ሴቶች መሆናቸውን አስታውቀዋል። በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት ኮሌጁ በመደበኛ ስልጠና 5 ሺህ 58 ሰልጣኞችን ለመቀበል አቅዶ 4 ሺህ 370 (86%) ሰልጣኞችን ማሰልጠን መቻሉን፣በአጫጭር ስልጠናዎች ደግሞ በስራ ፈጠራ (Entrepreneurship) 13 ሺህ 217 ለማሰልጠን አቅዶ 32 ሺህ (235%) እንዲሁም በቴክኒክ ክህሎት 5 ሺህ 400 አቅዶ 17 ሺህ 526 (324%) ዜጎችን በማሰልጠን ወደ ስራ ዓለም እንዲገቡ መደረጉን አመልክተዋል።
📅 2026-03-10 07:30:59
📅 2026-03-03 02:21:56
መድረኩን የከፈቱት የኮሌጅ ዲን የሆኑት አቶ ባሻዬ በየነ ሲሆኑ የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በሰባት ወር ዉስጥ የሠራውን የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት በዝርዝር አቅርበዋል፡፡\r\nየጥራት አስተዳደር ቡድን መሪ ኢንስትራክተር ተስፋዬ አያሌው የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ Iso ተሞክሮና በኮሌጅ ደረጃ የተሰሩ የdigitalization ስራዎች ላይ ገለፃ አድርጓል።\r\nየአልማዝ በም ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን የሆኑት አቶ ታደሰ ቅምስ የተቋማትን የዉስጥ አቅም ለማሳደግ ከሚሰሩ አዳዲስ እሳቤዎች አንፃር ኢንተርራይዝ ምስረታ ላይ ለተሰብሳቢዎች የሄዱበትን ሂደት ተሞክሮ የሰጡ ሲሆን በኮሌጅ ዉስጥም አራት ኢንተርፕራይዝ ተመስርቶ የስራ ዉል ስምምነት ኮሌጁና ኢንተርፕራይዙ ከፍትህ ጋር ዉሉን በማፅደቅ ህጋዊ ስምምነት አግኝቶ ወደ ስራ ገብቷል ብለዋል፡፡ \r\nአቶ ብረሃን አሰፋ ከይፋት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አይሶ ሰርተፍኬት ለማግኘት እየተሩ ያለዉን የትግበራ ሂደት ለተሰብሳቢዎች አቅርበዋል፡፡ \r\nተሳታፊዎቹም የኮሌጁን ቅጥር ግቢውን፣ መማሪያ ክፍሎችንና ወርክ ሾፖችን ተዛዙረው ጉብኝት አድርገዋል።\r\nበመጨረሻም በቀረበው ውይይት ላይ ጥያቄና አስተያየት በተሳታፊዎች የቀረበ ሲሆን ለቀረቡት ጥያቄዎች በኮሌጅ ዲን በአቶ ባሻዬ በየነ ማጠቃለያ የተሠጠ ሲሆን በቀጣይ መሠራት ያለባቸው ተግባራት ላይ አቅጣጫ ተሠጥቶ የእለቱ ውይይት ተጠናቋል።\r\n#ደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክ
Create your first notice to get started!