📅 2025-11-13 11:38:47(23 days ago)
በላይነህ ክንዴ ግሩፕ የፌቤላ የመኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካ ከደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና ከደብረ ብርሃን ዩንቨርሲቲ ተመርቀው የወጡ ሰላሳ ሰልጣኞችን ተቀብሎ የተግባር ስልጠና ለመስጠት ስምምነት አድርጓል። ስምምነቱ ፋብሪካው ከ2ቱ ተቋማት የመለመላቸውን ሰልጣኞች ለ4 ወራት አሰልጥኖ ለመቅጠር መሆኑም ተገልጿል። በመርሐ ግብሩ ላይ የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት እንዳሉት፤ በከተማው ወደ ማምረት የገቡ ብዙ ፋብሪካዎች ቢኖሩም የበላይነህ ክንዴ ግሩፕ ግን ሞዴል የሚሆን ተግባር እየፈጸመ ነው። በዚሁ ወቅት እንዳሉት ፋብሪካው ለአካባቢውን ወጣቶች የስራ እድል ከመፍጠር አኳያ ሀላፊነቱን እየተወጣ እንደሚገኝ ገልጸዋል። እንደዚህ አይነት የኢንደስትሪ ትስስሮች ተማሪዎች በተቋማቸው ከሚያገኙት የንድፈ ሀሳብ ስልጠና በተጨማሪ የተግባር ስልጠና ለማግኘት የሚያስችል ስለመሆኑ አንስተዋል። ይህንን ተግባር ሌሎች በከተማው የሚገኙ ኢንደስትሪዎች በተሞክሮነት በመውሰድ ሰልጣኞችን በመቀበል የተግባር ስልጠና እንዲያገኙ ማድረግ እንደሚገባቸውም አስገንዝበዋል። የበላይነህ ክንዴ ግሩፕ የፌቤላ ኢንዱስትሪያል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ እንየው ዋሴ እንደተናገሩት፤ ፋብሪካው የ2ቱን ተቋማት ሰልጣኞች የንድፈ ሀሳብ ስልጠና በመስጠት በቅጥር ለመውሰድና በሌሎች ስራዎች ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የማስቻል ስራ እየሰራ ነው ኢንዱስትሪውን ለማሳደግ ባለሙያው መሰልጠን ያለበት ከዩንቨርስቲና ከቴክኒክ ኮሌጅ ብቻ ሳይሆን ከኢንዱስትሪ ተቋማትም የተግባር ስልጠና መውሰድ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ባሻዬ በየነ እንደተናገሩት፤ በኮሌጁ የሰለጠኑ ሰልጣኞች ከሰለጠኑ በኋላ ወደ ኢንዱስትሪው እንዲገቡ ለማድረግ ይህ አይነት ስምምነት ያስፈልጋል። በሰልጣኞቹ የጋራ ስራ መስራት ስላለብንና ብቁ እንዲሆኑ ኢንዱስትሪው የራሱ ድርሻ አለበት ያሉ ሲሆን 2ቱም ባለድርሻ በመሆን እንሰራለን ብለዋል።
📅 2025-11-13 11:36:40(23 days ago)
የውይይቱ ዓላማ ኢንዱስትሪዎች ከቴክኒክና ሞያ ሰልጣኞች ሰልጥነው በሚወጡበት ሞያ ላይ በስልጠና በግብዓትና በገንዘብ በኩል ድጋፍ የሚያደርጉበትን ሁኔታ ለመግባባት እንዲሁም ከቴክኒክና ሞያ ኮሌጁ ሰልጣኞች በምን ዘርፍና ሞያ መሰልጠን እንዳለባቸው( የኢንዱስትሪዎችን ፍላጎት) ላይ መሆኑም ተመላክቷል፡፡ የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ባሻዬ በየነ እንደተናገሩት፤ ቴክኒክና ሞያ ኮሌጁ ከኢንዱስርሪዎች ጋር የሚያደርገው የጋራ ውይይት ወሳኝ ጉዳይ ነው፡፡ ኢንዱስትሪውም በክህሎት ላይ የትብብር ስልጠና እንዲሰጥ፣ ሰልጣኞች ማሽኖችን በተገቢው እንዲውቁ የራሳቸው ሚና እንዳላቸውም አስረድተዋል፡፡ ተቋማትና ኢንዱስትሪዎች በጋራ መክረው ያሉትን ክፍተቶች በመለየት የጋራ ምክር አድርገናን ብለዋል፡፡በውይይቱም ቴክኒክና ሞያ ኮሌጆች የሚያወጧቸው ሰልጣኞች ኢንዱስትሪዎች የሚፈልጉበትን አግባብ ያቀረቡ መሆኑንና ተቋሙም መረዳቱን ተናግረዋል፡፡ የአማራ ክልል ስራ ክህሎት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አማራ አለሙ እንደተናገሩት፤ የቴክኒክና ሞያ ኮሌጅ የንድፈ ሃሳብ ትምህርትን ከኢንዱስትርዎች የተግባር ትምህርት ጋር በማገናኘት ጥራት ያለው ሰልጣኝ ማውጣት ያስፈልጋል ከ40 በላይ የኢንዱስትሪ ባለቤቶች በውይይቱ መሳተፋቸውን የገለፁ ሲሆን፤ በዚህ ግንኙነት መሰረት ሰልጥነው የሚወጡ ወጣቶች የክሎት ክፍተት እንደማይኖራቸውም አስረድተዋል፡፡ ሰልጣኞች በቀጣሪ ድርጅቶች ፊት ቀርበው በሞያቸው እንዲያሰለጥኑ እድል ማግኘታቸውና የስራ እድልም እንደሚፈጠርላቸው መደረጉ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል፡፡ የተስፋ ኢንተርፕራይዝ ድርጅት ፕሪጀክት ማናጀር ስራ አስኪያጅ አቶ ፍሬው ደሳለኝ እንደገለፁት፤ ኢንዱስትሪዎችና ቴክኒክና ሞያ ኮሌጆችን አንድ ላይ በማድረግ የስልጠና ጥራት እንዲሻሻል ስራዎችን እየሰራ ይገኛል ውይይቱ ቴክኒክና ሞያ ኮሌጆች ከኢንዱስትሪዎች ጋር ተቀራርበው እንዲሰሩ ለማድረግ ያለመ ሲሆን በዚህ መልኩ 2ቱ በስምምነት ሰልጣኖችን እንዲያበቁና የስራ እድል እንዲፈጥሩ የሚያግዝ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡ ድጅቱ በደብረ ብርሃን ከተማ በዚህ ዓመት ከ5 ሺ በላይ ወጣቶችን በተለያዩ ብድርና ስልጠና የሚደግፍ መሆኑንም አስረድተዋል ድርጅቱ በ5 ዓመት ጊዜ ውስጥ በክህሎት ስልጠና ላይ 200ሺ ወጣቶችን እንደ ሀገር ለማሰልጠን ያቀደ ሲሆን ግማሽ ጊዜውን አጠናቋል ብለዋል፡፡ በመርሐ ግብሩ ላይ የኢንዱስትሪ ባለቤቶች፣ የደብረ ብርሃን ከተማ ስራ ክህሎት አመራሮች፣ ተመራቂ ተማሪዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡
📅 2025-10-11 08:46:08
ገበያ ተኮር በሆኑ የስራ ዘርፎች ወጣቶችን በአጫጭር ስልጠና በማብቃት ወደ ስራ እንዲገቡ እየተደረገ ነው። በተያዘው በጀት ዓመትም ከ19ሺህ 2መቶ በላይ ወጣቶች ገበያ ተኮር በሆኑ አጫጭር ስልጠናዎችና ቴክኒካል ስልጠና ወደ ስራ ለማስገባት ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን በማንሳት ከአምሪፍ ሄልዝ አፍሪካ ጋር በመተባበር ለአንድ ወር በቧንቧ መስመር ዝርጋታና በኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ የሰለጠኑ 50 ሰልጣኞች ዛሬ በደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ተመርቀዋል። ከአምሪፍ ኸልዝ አፍሪካ ጋር ውል ገብቶ ወጣቶቹን ያሰለጠነው የደብረብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ባሻዬ በየነ በበኩላቸው ሰልጣኞች በተመረጡ የሙያ ዘርፎች ተገቢውን ተግባር ተኮር ስልጠና ወስደው 99ከመቶ የሚሆኑትም የሲኦሲ ምዘነውን በብቃት አጠናቀው የተመረቁ መሆናቸውን ገልፀዋል። የደብረብርሃን ከተማ ስራና ስልጠና መምሪያ ሀላፊ ወ/ሮ አይናለም ከፈለኝ እንዳሉት ስራ አጥ ዜጎችን በተለያዩ የስልጠና ዘርፎች የቴክኒካል እና የአጫጭር ስልጠናዎች አሰልጥኖ ወደ ስራ ለማስገባት ከመንግስት አቅም ባለፈ የተለያዩ ግብረሰናይ ድርጅቶች ጋር በመቀናጀት እየተሰራ ነው ብለዋል። የወሰድነው ስልጠና ተግባር ተኮር በመሆኑና ለስራ መነሻ የሚሆን ግብዓትም ከአምሪፍ በማግኘታችን በራስ አቅም ወደ ስራ ገብተን ከራሳችን ባለፈ ለሌሎችም የስራ እድል ለመፍጠር እንሰራለን ያሉት ደግሞ ያነጋገርናቸው ሰልጣኞች ናቸው። (የፖ/ሊ / ኮ/ ህዝብ ግንኑነት)
📅 2025-09-24 05:12:43
📅 2025-08-12 11:04:07
Create your first notice to get started!