📅 2026-03-10 07:30:59(8 days ago)
📅 2026-03-03 02:21:56(15 days ago)
መድረኩን የከፈቱት የኮሌጅ ዲን የሆኑት አቶ ባሻዬ በየነ ሲሆኑ የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በሰባት ወር ዉስጥ የሠራውን የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት በዝርዝር አቅርበዋል፡፡\r\nየጥራት አስተዳደር ቡድን መሪ ኢንስትራክተር ተስፋዬ አያሌው የደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ Iso ተሞክሮና በኮሌጅ ደረጃ የተሰሩ የdigitalization ስራዎች ላይ ገለፃ አድርጓል።\r\nየአልማዝ በም ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን የሆኑት አቶ ታደሰ ቅምስ የተቋማትን የዉስጥ አቅም ለማሳደግ ከሚሰሩ አዳዲስ እሳቤዎች አንፃር ኢንተርራይዝ ምስረታ ላይ ለተሰብሳቢዎች የሄዱበትን ሂደት ተሞክሮ የሰጡ ሲሆን በኮሌጅ ዉስጥም አራት ኢንተርፕራይዝ ተመስርቶ የስራ ዉል ስምምነት ኮሌጁና ኢንተርፕራይዙ ከፍትህ ጋር ዉሉን በማፅደቅ ህጋዊ ስምምነት አግኝቶ ወደ ስራ ገብቷል ብለዋል፡፡ \r\nአቶ ብረሃን አሰፋ ከይፋት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አይሶ ሰርተፍኬት ለማግኘት እየተሩ ያለዉን የትግበራ ሂደት ለተሰብሳቢዎች አቅርበዋል፡፡ \r\nተሳታፊዎቹም የኮሌጁን ቅጥር ግቢውን፣ መማሪያ ክፍሎችንና ወርክ ሾፖችን ተዛዙረው ጉብኝት አድርገዋል።\r\nበመጨረሻም በቀረበው ውይይት ላይ ጥያቄና አስተያየት በተሳታፊዎች የቀረበ ሲሆን ለቀረቡት ጥያቄዎች በኮሌጅ ዲን በአቶ ባሻዬ በየነ ማጠቃለያ የተሠጠ ሲሆን በቀጣይ መሠራት ያለባቸው ተግባራት ላይ አቅጣጫ ተሠጥቶ የእለቱ ውይይት ተጠናቋል።\r\n#ደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክ
📅 2026-02-13 01:47:41
በደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሠጠ። ቀን 5/06/2018ዓ.ም ደብረ ብርሀን በደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በዛሬው ዕለት ለኮሌጁ አሰልጣኞችና የአስተዳደር ሰራተኞች የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና በመስጠት ላይ ይገኛል ። ስልጠናውን ያስጀመሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ባሻዬ በየነ ሲሆኑ ስልጠናው ለተከታታይ ሦስት ቀናቶች የሚወስድ ሲሆን የተቋሙን የማስፈጸም አቅም ለማሳደግ ፣ አሠራሮችን ለማዘመንና ግንዛቤ ለማዳበር ያግዛል ብለዋል። በኮሌጁ ሰው ሀብት አስተዳደር ቡድን መሪ በአቶ አንተነህ ታሪኩ አማካኝነት የሰራተኞች ትምህርት ማስረጃዎች ማጣራትን በተመለከተ እና በመልካም አስተዳደር በአገልግሎት አሰጣጥ እንዲሁም የኢንስትራክተሮች ዝዉዉር ምደባ መመሪያን ያተኮረ ስልጠና እየተሰጠ ነው። በተጨማሪም የስራ ስነ- ምግባር ላይ በወ/ሮ ውዴ ሀይሉ በስነ ምግባር ባለሙያ የቀረበ ሲሆን ስልጠናውም በነገው እለት ቀጥሎ ይውላል። # ደብረ ብርሃን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
📅 2026-02-09 03:05:58
📅 2026-02-05 02:44:28
Create your first notice to get started!